image
image
image
image
image

የልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት ወረዳን መሰረት ያደረገ የጤናው ዘርፍ ዕቅድ ለሁሉም ጤና ጣቢያዎች እያሳቀደ ነው፡፡

ሰኔ 26, 2017
ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም የልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት ወረዳን መሰረት ያደረገ የጤናው ዘርፍ ዕቅድን ለ8ቱም ጤና ጣቢያዎች በክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት በየቡድኑ አስተባባሪዎች በመደገፍ እቅዱ ተመሳሳይነትና ወጥነት ባለው መልኩ ማሳቀድ ጀምሯል። በዕቅድ ማሳቀዱ ማስጀመሪያው ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክፍለ ከተማው ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አህመድ እንድሪስ ጤና ጽ/ቤቱ በስሩ የሚገኙ የጤና ተቋማት ዕቅድ እና አፈጻጸም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መሆኑን ገልጸው የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ሲታቀደም ይህንን መሰረት ያደረገ መሆን እንደላበት ተናግረዋል፡፡ የክፍለ ከተማው ጤና ጽ/ቤት የኳሊቲ ቡድን መሪ የሆኑት ሲ/ር ትግስት በቀለ በበኩላቸው የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አዘገጃጀት በክፍለ ከተማው ጤና ጽ/ቤት እና በስሩ በሚገኙ የጤና ጣቢያዎች ወጥነት ያለው እንዲሆን በትኩረት ተናበን የጠራ እቅድ ማቀድ አለብን ብለዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ