image
image
image
image
image

በልደታ ክ/ከተማ የማህፀን በር ካንሰር መከላከያ ክትባት መሰጠት ተጀመረ።

ታህሳስ 21, 2017
የክ/ከተማው ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አህመድ እንድሪስ ባስተላለፍት መልዕክት የማህፀን በር ካንሰር በሴቶች ላይ እያደረሰ ያለውን የጤና ችግር ለመከላከል መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ብለው በዚህም ከዛሬ ከ21/4/17 እስከ 25/4/17 ዓ.ም ድረስ ክትባቱ መሰጠት መጀመሩን ተናግረዋል። አቶ አህመድ አክለውም እድሚያቸው ከ9 ዓመት እስከ 14 ዓመት ያሉ ሴቶች ክትባቱን መውሰድ አለባቸው ያሉ ሲሆን ክትባቱም በትምህርት ቤቶች፣ በጤና ተቋማትና ቤት ለቤት እንደሚሰጥም ገልፀዋል። የዋና ስራ አስፈፃሚ የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ የሆኑት አቶ ጌታሁን ሀይለማሪያም በበኩላቸው ሴቶች ክትባቱን በመውሰድ እራሳቸውን ከበሽታው መጠበቅ እንዳለባቸው ገልፀው ወላጆችም ክትባቱ ስኬታማ እንዲሆን የተለመደውን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉም አአሳስበዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ