image
image
image
image
image

በልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት አስተባባሪነት ሲሰጥ የቆየው የተቀናጀ የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባት ዘመቻ በ102 ፐርሰንት አፈጻጸም በስኬት ተጠናቀቀ።

ግንቦት 28, 2017
ል/ክ/ከተማ ጤና ጽ/ቤት ግንቦት 27/2017 ዓም በከተማችን አዲስ አበባ ብሎም በልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት በአስሩም ወረዳ በ8ቱ ጤና ጣቢያዎች ከግንቦት 18 እስከ 27 / 2017 ዓ.ም ለተከታታይ አስር ቀናት እድሜያቸው ከ9 ወር እስከ 5 አመት ለሆናቸው ህጻናት ሲሰጥ የቆየው የተቀናጀ የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባት 102% በመክተብ በተሳካ አፈጻጸም ተከውኗል። ክፍለ ከተማው በስሩ ባሉ ባሉ 8 ጤና ጣቢያዎች እና በተመረጡ ጊዜያዊ የክትባት መስጫ ጣቢያዎች 23,915 ህጻናትን ለመክተብ ታቅዶ 24,330 ህጻናት በመክተብ 102% ክንውን አሳይቷል። የክትባት ዘመቻውን በመምራትና በማስተባበር ሁሉንም ባለድርሻ አካላትን ያመሰገኑት ዛሬ በመዝጊያ ፕርግራሙ ላይ የተገኙት የጽ/ቤቱ ሃላፊ አቶ አህመድ እንድሪስ በዚህ ክትባት ዘመቻ ወላጆች ወይም አሳዳጊዎች ልጆቻቸውን በማስከተባቸው፣ ባለሙያው ላደረገው እርብርብ፣ የጤና ቢሮ አስተባባሪዎች ላደረጉት እገዛ እና የየጤና ጣቢያዎች አመራሮችን ሁሉንም ለተመዘገበው ስኬት እውቅና የሰጡ ሲሆን ሃላፊው ሃሳባቸውን ሲቋጩም ስለቻልን ነው ስኬት ያስመዘገብነው። በሌሎችም ስራዎች የተሻልን መሆናችንን ማሳየት አለብን ብለዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ